ሀባሪ ሜዲካል ፕላዛ ተመርቆ ስራ ጀመረ

Date:

ማዕከሉን የመረቁት ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ናቸው።

የተሻለ ህክምና ፍላጋ ወደተለያዩ ሀገራት ከኢትዮጵያ በሚደረግ ጉዞ በአመት ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚወጣ በምርቃት ስነስርዓቱ ላይ ተነግሯል።

አብዛኛው የውጭ ሀገር ህክምና ጉዞ ሙሉ የጤና ምርመራ ለማድረግ እና የካንሰር ህክምና ፍለጋ መሆኑ ተጠቅሷል።

ሀባሪ ሜዲካል ፕላዛ የተቋቋመውም ይህንን በህክምና ምክንያት ወደ ወጪ ሀገር የሚደረግን ጉዞ ማሰቀረት ብሎም ከጎረቤት ሀገራት ታካሚዎችን ለመሳብና አዲስ አበባን የህክምና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ነው ሲሉ የማዕከሉ መስራችና ባለቤት ዶ/ር አከዛ ጣዕመ ተናግረዋል።

በስነስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት ከንቲባ አደነች አበቤ በከተማዋ ያለውን የጤና አቅርቦት ለማሳደግ መንግስት ነባሮቹን የጤና ተቋማት አቅማቸውን ማሳደግ ላይ እንዲሁም አዳዲስ ሆስፒታሎች ግንባታ እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

በዚህም ሶስት አዳዲስ ሆስፒታሎች እየተገነቡ መሆኑን ተናግረው በዚህም የግሉ ዘርፍ አብሮ እንዲሰራ ጠይቀዋል።

ዛሬ የተመረቀው ሀባሪ ሜዲካል ፕላዛ አይነት ተቋማት በብዛት እንደሚያስፈልጉ አስረድተዋል ።

የውስጥ ደዌ፣ የህፃናት፣ የማህፀን እና የፅንስ፣ የቆዳ ህክም፣ የልብና ሌሎች  ህክምናዎችን ጨምሮ 15 ስፔሻሊስት ህክምናዎች እንደሚሰጥ የተናገረው ሀባሪ ሜዲካል ፕላዛ የቪአይፒ የህክምና ፓኬጆች ማሰናዳቱንም ተናግሯል።

ማዕከሉ ሙሉ ለሙሉ ተመላላሽ ታካሚዎች የሚያስተናግድ ሲሆን ተኝቶ ህክምና የሚያስፈልጋቸው ሲኖሩ ወደ እህት ኩባንያዎቹ   አሜሪካን ሜዲካል ፣ሰማሪታን ሰርጀሪካል ሴንተር እና አክሶን ስትሮክ እና ስፓይን ሴንተር እንደሚልክ ዶ/ር አከዛ አስረድተዋል።

ሀባሪ ሜዲካል ፕላዛ 500 መቶ ሚሊየን ብር  ኢንቨስት አድረጉ ስራ መጀመሩን ሰምተናል።

ሀባሪ ሜዲካል ፕላዛ  የተከፈተው በሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ አቅራቢያ ኖክ ሕንፃ ላይ ነው።

ሸገር 102.1 ንጋቱ ሙሉ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ የኢራን የኒውክሌር ተቋም ላይ ጥቃት ለማድረስ ዛቱ

አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርሰው ጥቃት 11ኛ ቀኑን ይዟል። ፕሬዝዳንት...

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአሜሪካ ” American Space ” ማዕከል ተመረቀ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቨን ማሲንጋ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመውን "American...

አሐዱ ባንክ ለ 8ኛ ጊዜ የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናወነ

አሐዱ ባንክ ሥራ የጀመረበትን 4ኛ ዓመት በማስመልከት የተለያዩ ኩነቶችን...

ዕንባ ጠባቂ ከቀረቡለት አቤቱታዎች 84% በመንግስታዊ ተቋማት ላይ የቀረቡ ናቸው

የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በተጠናቀቀው የ2018 በጅት ዓመት...