- ተወዳጅና ታዋቂ የፊልም ተዋንያንና ዳይሬክተሮች ስልጠናውን ይሰጣሉ።
የፊልም ትምህርትን በዲግሪ ደረጃ ለማስተማር ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመጀመሪያና ብቸኛ የሆነው ልቀት ኮሌጅ ለ2017 ክረምት አጭርና እጅግ ውጤታማ የስልጠና መርሐ ግብር ማዘጋጀቱን ጠቁሟል ።
ስልጠናውን በአክቲንግ የስልጠና ዘርፍ ተዋናይ ግሩም ኤርሚያስ፣ በዳይሬክቲንግ ስልጠና ዳይሬክተር ሄኖክ አየለ፣ በሲኒማቶግራፊ ዘርፍ ሲኒማቶግራፈር ቢሊ መኮንን እንዲሁም ለስክሪን ፕሌይ ራይቲንግ ስልጠና የፊልም መምህሩ ዮሴፍ ሀይሉ ይሰጣሉ።
ስልጠናው በመጪው ቅዳሜ ሀምሌ 12 ቀን 2017 ዓ.ም መሰጠት የሚጀምር ሲሆን ቅዳሜና እሁድ በቀን መርሐ -ግብር ለተከታታይ ሳምንታት ይሰጣል፤ ስልጠና መውሰድ የሚፈልጉ አራት ኪሎ ከትምህርት ሚኒስቴር ጀርባ ኢክላስ ህንፃ 3ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የኮሌጁ አድራሻ በመምጣት ወይም በ0984717144 እና በ0940089999 መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል።
