ሲኤንኤን የኢትዮጵያን የአቪየሽን እምርታ አደነቀ

Date:

የዓለማችን ታዋቂው የዜና ማሰራጫ ሲኤንኤን፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድን አስደናቂ የዕድገት ጉዞ በሰፊው ዘገበ።

በ12.5 ቢሊዮን ዶላር በቢሾፍቱ ከተማ እየተገነባ ያለው ግዙፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ ከፍተኛ አቅም እንደሚኖረው ዘገባው አሳይቷል።

ይህ ዘመናዊ ፕሮጀክት አፍሪካውያንን በአንድነት በማስተሳሰር እና የአህጉሪቱን ነፃ ንግድ ለማፋጠን ትልቅ ሚና እንዳለው ተገልጿል።

ይህ ግዙፍ የልማት ሥራ ኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ ትስስር እና የንግድ ማዕከል እንደሚያደርጋት ሲኤንኤን አመልክቷል።

አየር መንገዱ ከአቪየሽን ሥራው ጎን ለጎን የኢትዮጵያን ውብ ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ሀብቶች ለዓለም በማስተዋወቅ የቱሪዝም ገቢዋ እንዲያድግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ዘገባው ጠቁሟል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...