ከአሌክስ አብርሃ
((አገርህን ስታፈርስ የሚጠብቅህ ይሄ ነው)) የፈለክበት ደረጃ ብትደርስ ጥራጊ ነህ! ባለቤቱን ካስቀየምክ የፈለገውን ይልሃል! ለሱማሊያዊያን እንደዚህ ጊዜ አሳዛኝና አሳፋሪ ጊዜ ያለ አይመስለኝም።
ትራምፕ ለካቢኒያቸው “ትውልደ ሱማሊያዊቷን ኢልሃን ኡመር ያውም “ኮንግረስውማን” የሆነችውን ሴትዮ እንዳትበላ እንዳትዘራ አድርገው ወርደውባታል! እደግመዋለሁ እንዲህማ ተብየ የምበላው እንጀራ ባፍንጫየ ይውጣ ብለህ የምትመለስበት አገር እስከማይኖርህ አገርህን አታፍርስ!
በነገራችን ላይ ትራምፕ የተናገሩበት መንገድ ፀያፍ ቢሆንም ሱማሊያውያኑ በስፋት በህገወጥ መንገድ የመንግስትን ገንዘብ በመውሰድ ግብር በማጭበርበር፣ የውሸት ጋብቻና ቪዛ ጉዳዮች ላይ በማጭበርበር፣ ታጣቂወችን በመርዳት፣ በስፋት ስማቸው ይነሳል።
((( ከሱሚሊያዊያኑ ቀጥሎ በተለይ በተጭበረበረ ሰነድና ጋብቻ ወደአሜሪካ በመምጣት ቀጣዮ አገር ማን እንደሆነ ሆድ ይፍጀው))) ለሰው ብሎ ሲያማ ለኔ ብለህ ስማ! ወደትራምፕ ንግግር!
“ኢልሃንኮ ቆሻሻ ናት፣ አዎ ቆሻሻ ናት! ጓደኞቿም ቆሻሻ ናቸው…አገራችን ላይ ላያቸው አልፈልግም፤ አንፈልጋቸውም! ሰው ከገት መጥቶ አይ ይሄ አገር ገነት አይደለም ብሎ ቢያማርር እሽ …ከሲኦል መጥቶ ስለገነት ያወራል? …አገሯኮ ምንም የለም ምንም ፤ ቆሻሾች ናቸው!
አገራቸው ግማታም ነው ቆሻሻ! ካለምክንያት እንዳይመስላችሁ አገራቸው ዋጋ ቢስ የሆነው፤ በዚህ ባህሪያቸው ነው። ሰወች የምትለው ስህተት ነው ሊሉ ይችላሉ፤ በዚህም አለ በዚያ በተሳሳተም መንገድ ቢሆን ቆሻሻውን ከአገራችን ላይ ማፅዳት አለብን።
አገራችን ለውጥ ላይ ናት! ወሳኝ ጊዜ ላይ ነን። ይሄን ነገር ሌሎችም አገራት ላይ ልናገረው እችላለሁ። ጠራርጎ ማባረርና ነገሩን ማስተካከል ነው በቃ! “
