ከ2015 ጀምሮ ወደ ጣሊያን ለመሻገር የሞከሩ 3500 ህፃናት መሞታቸውን ወይም የገቡበት አለመታወቁን ዩኒሴፍ አስታውቋል።
ከህፃናቱ በተጨማሪ 20,800 ሰዎች በተጠቀሰው አመት ውስጥ በባህሩ ላይ ህይወታቸውን እንዳጡ አስታውቋል።
ትክክለኛ ቁጥሩ ከዚህም ሊበልጥ እንደሚችል ያሳወቀው ዩኒሴፍ ሜድትራንያን ተሻግረው ጣሊያን ለመግባት ከሚሞክሩት መሃል 17% ያህሉ ህፃናት መሆናቸውንም ገልጿል።
ከህፃናቱ ውስጥ 70 በመቶዎች ለብቻቸው አስፈሪውን ጉዞ እንደሚያደርጉ የገለፀው ዩኒሴፍ ህፃናቱ ከጦርነት እና ከአስከፊ ድህነት ለመራቅ ጉዞውን እንደሚያደርጉ ገልጿል።
ዩኒሴፍ በየቀኑ በሜድትራንያን ባህር ላይ የአንድ ህፃን ህይወት ያልፋል ያለ ሲሆን ሁሉም አካላት የህፃናት እና የንፁሃን ዜጎች ደህንነት እንዲረጋገጥ እንዲሰሩ ጥሪውን አቅርቧል።
