በሜድትራንያን ባህር ላይ ከ3,500 በላይ ህፃናት መሞታቸውን ዩኒሴፍ አስታውቋል

Date:

ከ2015 ጀምሮ ወደ ጣሊያን ለመሻገር የሞከሩ 3500 ህፃናት መሞታቸውን ወይም የገቡበት አለመታወቁን ዩኒሴፍ አስታውቋል።

ከህፃናቱ በተጨማሪ 20,800 ሰዎች በተጠቀሰው አመት ውስጥ በባህሩ ላይ ህይወታቸውን እንዳጡ አስታውቋል።

ትክክለኛ ቁጥሩ ከዚህም ሊበልጥ እንደሚችል ያሳወቀው ዩኒሴፍ ሜድትራንያን ተሻግረው ጣሊያን ለመግባት ከሚሞክሩት መሃል 17% ያህሉ ህፃናት መሆናቸውንም ገልጿል።

ከህፃናቱ ውስጥ 70 በመቶዎች ለብቻቸው አስፈሪውን ጉዞ እንደሚያደርጉ የገለፀው ዩኒሴፍ ህፃናቱ ከጦርነት እና ከአስከፊ ድህነት ለመራቅ ጉዞውን እንደሚያደርጉ ገልጿል።

ዩኒሴፍ በየቀኑ በሜድትራንያን ባህር ላይ የአንድ ህፃን ህይወት ያልፋል ያለ ሲሆን ሁሉም አካላት የህፃናት እና የንፁሃን ዜጎች ደህንነት እንዲረጋገጥ እንዲሰሩ ጥሪውን አቅርቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ የኢራን የኒውክሌር ተቋም ላይ ጥቃት ለማድረስ ዛቱ

አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርሰው ጥቃት 11ኛ ቀኑን ይዟል። ፕሬዝዳንት...

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአሜሪካ ” American Space ” ማዕከል ተመረቀ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቨን ማሲንጋ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመውን "American...

አሐዱ ባንክ ለ 8ኛ ጊዜ የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናወነ

አሐዱ ባንክ ሥራ የጀመረበትን 4ኛ ዓመት በማስመልከት የተለያዩ ኩነቶችን...

ዕንባ ጠባቂ ከቀረቡለት አቤቱታዎች 84% በመንግስታዊ ተቋማት ላይ የቀረቡ ናቸው

የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በተጠናቀቀው የ2018 በጅት ዓመት...