የቀድሞው የኢትዮጵያ ውሃ ስፖርቶች ፌደሬሽን ፕሬዝደንት የነበሩት አቶ ኪሮስ ሀብቴ አጠቃላይ ከተሰጠው 12 ድምጽ 9 ድምፅ በማግኝት አሸንፈዋል።
በኦሮሚያ ክልል የተወከሉት አቶ ኪሮስ ሀብቴ ከአሁን በፊት ተቋሙን ለ8 አመታት በፕሬዝዳንትነት መምራታቸውም ይታወሳል።
በፕሬዝዳንትነት ዘመናቸውን በሪዮ ኦሎምፒክ ልጃቸው ሮቤል ኪሮስን እንዲሳተፍ በማድረግ ወቀሳ ሲቀርብባቸው እንደነበርም አይዘነጋም።
በወቅቱ ሮቤል ኪሮስ ካስመዘገበው ደካማ ውጤት ባሻገር በነበረው ተክለ ሰውነት የዓለም አቀፍ ሚዲያዎች መነጋገሪያ እንደነበር ይታወሳል።
