በቀነኒ አዱኛ ሞት ዙሪያ ፖሊስ የምርመራ ውጤቶች አሁንም አልደረሱኝም አለ

Date:

በፍቅር አጋሩ ቀነኒ አዱኛ ግድያ ተጠርጥሮ በእስር ላይ የሚገኘው ድምጻዊ አንዱአለም ጎሳ በዛሬው ዕለት በአራዳ ምድብ ችሎት ለሦስተኛ ጊዜ የቀረበ ሲሆን፤ ፖሊስ በችሎቱ “የፌደራል ፖሊስ ፎረንሲክ የምርመራ ውጤቶቹ አሁንም አልደረሱኝም” በማለት 14 ቀን ተጨማሪ ቀናት ጠይቋል።

በዛሬው ዕለት በችሎቱ የፖሊስ የምርመራ ውጤት ይጠበቅ የነበረ ቢሆንም ፖሊስ የ15 ሰዎች መረጃ ማሰባሰቡን በመግለጽ፤ ነገር ግን ፎረንሲክ የምርመራ ውጤቶቹ ስላልደረሱት ተጨማሪ ቀናትን ጠይቋል።

የአንዱዓለም ጠበቃ በበኩሉ የቀነኒ ዲያሪ እሱ ጋር እንዳለ ጠቅሶ፤ ቀነኒ ሯሷን ለማጥፋት በተደጋጋሚ መድኃኒት ወስዳ እንደነበር ተፅፎ ማግኘቱን አስታውቋል።

“ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ መፈቀድ የለበትም! አንዱዓለም የዋስ መብቱ ሊጠበቅለት ይገባል” ብሎ ተከራክሯል።

በተጨማሪም “ከእስር ወጥቶ የሙዚቃ ስራውን ለፋሲካ ያቅርብ የሚለው የዩቲዩብ ዘገባ የተሳሳተ ነው ሊታረም ይገባል” ብሏል።

ፍርድ ቤት የሁለቱን ክርክር በመስማት የክርክሩን ውሳኔ ለመስጠት ለነገ ማክሰኞ ጠዋት ቀጥሮ ሰጥቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...

“ሎዛ ዘፀአት”እና “የሎዛ ድርሳናት”ተከታታይ ረጅም ልቦለድ መጻሕፍት ተመረቁ

በጋዜጠኛና ደራሲ መርዕድ እስጢፋኖስ የተጻፉት ሎዛ ዘፀአት(2014 ዓ.ም) እና...