በባንኮች መካከል የውጭ ምንዛሬ መገበያየት የሚያስችል የግብይት አውታር ተጀመረ

Date:

በሀገሪቱ የፋይናንስ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ አውቶሜትድ ሥርዓት የሚካሄደው ግብይቱ በኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ መድረክ ላይ ሁሉም ንግድ ባንኮች ስለ ገበያው እኩል መረጃ ኖሯቸው የሚከናወን መሆኑን ብሔራዊ ባንክ በይፋዊ መግለጫው አስታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ፣ “ለተሳታፊ ሁሉ ግልጽ፣ ፈጣንና በመመሪያ የተመራ የገበያ አካባቢ ይፈጥራል። መድረኩ የገበያ ዲሲፕሊንን ለማጠንከር፣ የዋጋ ሂደትን ለማሻሻልና የፋይናንስ ገበያ ሪፎርምን ለመደገፍ ትልቅ ግብዓት ነው።” ሲሉ በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ ተናግረዋል፡፡

የገበያው አሠራር በብሔራዊ ባንክ መመሪያዎች የሚመራ ሲሆን፣ ሁሉም ተሳታፊ ባንኮች የተቀመጡ የሥነ-ምግባር ደንቦችን እና የውጭ ምንዛሬ ተጋላጭነት ገደቦችን የማክበር ግዴታ እንዳለባቸው ተጠቁሟል።

ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ገበያ ከዓለም አቀፍ አሠራሮች ጋር ለማጣጣም እና የውጭ ምንዛሬ አስተዳደርን ይበልጥ ዘመናዊ ለማድረግ ያለመ መሆኑም ተመላክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...