በትግራይ ክልል 7ኛው ጠቅላላ ሐገራዊ ምርጫ ይከናወናል

Date:

ሀገር አቀፍ የሕግ አውጪዎች የጋራ ምክክር መድረክ ላይ ገለፃ የሰጡት የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ንዋይ፥ በትግራይ ክልል ምርጫ ይደረጋል ወይ? የሚደረግ ከሆነስ ምን ያህል ዝግጅት ተደርጓል? የሚሉ ጥያቄዎችን አስተናግደዋል።

ምክትል ሰብሳቢው በምላሻቸው በክልሉ ምርጫው እንደሚደረግ አስታውቀዋል።

ጉዳዩን በተመለከተም ከክልሉ ጊዜያዊ መስተዳድርና በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፖርቲዎች ጋር ውይይት መደረጉን ስለመግለፃቸው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያጋራው መረጃ ይጠቁማል።

7ኛውን ጠቅላላ ሐገራዊ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለማካሄድ የታቀደ ሲሆን፥ የምርጫው ውጤት ደግሞ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ እንደሚደረግ ይጠበቃል።

የአራዳ ኤፍ ኤም

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...