ከኢራን ጋር የሚደረገው ጦርነት ገና አላበቃም ሲሉ የእስራኤል ጦር ዋና አዛዥ ኢያል ዛሚር ተናገሩ።
ኢራንና አጋሮቿ በእኛ እይታ ውስጥ ናቸው ሲሉ በወታደራዊ ግምገማ ስብሰባ ወቅት ተናግሯል። በኢራን ላይ የሚካሄደው ዘመቻም አላበቃምም ብለዋል።
በጋዛ የሚካሄደው ጦርነት የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት ያደረገው እጅግ ውስብስብ ጦርነት መሆኑን ጠቅሰው በጦርነት ብዙ ዋጋ እየከፈልን ነው፤ ዓላማችንን ከግብ ለማድረስ መስራታችንን እንቀጥላለን ብለዋል።
ከጥቂት ወራት በፊት እስራኤል በኢራን የኒኩሊየር ተቋማት ላይ በፈፀመችው ድንገተኛ የአየር ጥቃት ሁለቱ ሀገራት ወደ ሙሉ ጦርነት መግባታቸው ይታወቃል። በጦርነቱ አሜሪካ ከእስራኤል ጎን በመሰለፍ ኢራን ላይ መጠነ ሰፊ የአየር ጥቃት ፈፅመለች።
የሁለቱ ሀገራት ጦርነት ከ12 ቀናት በኃላ በተኩስ አቁም ስምምነት የተቋጨ ቢሆንም ዳግም ሊቀሰቀስ የሚችልበት ዕድል እንዳለ ይነገራል።
