አንዳንድ ሰዎች በኢትዮጵያና በኤርትራ መሀከል ችግር የተፈጠረዉ የኢትዮጵያ መንግስት የቀይ ባህር ጥያቄ ስላነሳ ነዉ የሚሉ ወሬዎች መኖራቸዉን አንስተዉ እዉነታዉ ግን ይህ አይደለም ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ችግር በትግራይ ጦርነት ወቅት የተጠነሰሰ እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
ግጭቱ በትግራይ ጦርነት ወቅት ከኤርትራ ጦር ዘረፋ እና ግድያ ጋር ተያይዞ የተጀመረ እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተናግረዋል፡፡
በአድዋ ከተማ ፋብሪካ ሲዘርዱ እንደነበርና አዲግራትም በተመሳሳይ ይህን ድርጊት ሲፈጸም እንደነበረ አንስተዉ፤ የኢትዮጵያ መንግስት በሰዓቱ በሁለቱም በኩል መዋጋት እንዳልቻለ ተናግረዋል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 10ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄ ነዉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመንግስትን የ2018 በጀት ዓመት በ6 ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በሚያቀርቡ ወቅት ነዉ ይህን ያሉት።
ይህንን ችግር ለመፍታት የተለያዩ የመንግስት አካላት ኤርትራ ሄደዉ እንደነበረና ምንም መፍትሄ ግን እንዳላመጡ ገልፀዋል።
የቀድሞዎቹን የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ደመቀ መኮንን እና ገዱ አንዳርጋቸውን ወደ ኤርትራ ልከው ሕዝቡን እንዳያጎሳቁሉ መጠየቃቸውንም ለፓርላማዉ ተናግረዋል፡፡
