በደቡብ አፍሪካ የቬንዳ ቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን በቃጠሎ አደጋ ወደመ

Date:

በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ባልታወቀ ምክንያት በተነሳ እሳት ሙሉ በሙሉ በቃጠሎ መውደሙ ተገለጸ።

በደቡብ አፍሪካ የቬንዳ ቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን በቃጠሎ አደጋ መውደሙ ተሰምቷል።

በደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት የምትገኘው የቬንዳ ቅዱስ ሩፋኤል መቃኞ ቤተክርስቲያን በትላንትናው ዕለት በደረሰ ድንገተኛ የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ መውደሟ ተረጋግጧል።

ቃጠሎው የተነሳው በሌሊት በመሆኑና በወቅቱ እርዳታ ማግኘት ባለመቻሉ፣ በቤተክርስቲያኗ ውስጥ የነበረው ንብረት ሁሉ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል። የአደጋው መነሻ እስካሁን አልታወቀም።


የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን ብርሃኑ ተክለያሬድ በአደጋው ሥፍራ ተገኝተው ምእመናንን አጽናንተዋል ።


ይህ በመንፈሳዊ አገልግሎቱና በምዕመናን አንድነት የምትታወቀው ቤተክርስቲያን ላይ የደረሰው አደጋ በደቡብ አፍሪካ ለሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ ታላቅ ሃዘን ሆኗል።

© Eotc Medhanalem

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...