
▪️ ሁለቱ መሪዎች በዩክሬን ሰላም እና የተኩስ ማቆም አስፈላጊነት ላይ ተወያይተዋል።
▪️ መሪዎቹ ወደ ሰላም የሚደረገው ሂደት በኃይል እና በመሠረተ ልማት ተኩስ አቁም እንዲጀመር ተስማምተዋል።
▪️ ፕሬዝዳንቶቹ በጥቁር ባህር የማሪታይም የተኩስ አቁም ንግግር “በአፋጣኝ” በመካከለኛው ምስራቅ እንዲጀመር ተስማምተዋል።
▪️ ፑቲን እና ትራምፕ በአሜሪካ እና በሩሲያ መካከል ያለው የተሻሻለ የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደፊት ትልቅ ጥቅም እንደሚኖረው መግባባት ላይ ደርሰዋል።
▪️ የሩሲያ እና አሜሪካ መጪው ግንኙነት “ግዙፍ የኢኮኖሚ ስምምነቶችን” እና የጂኦፖለቲካዊ መረጋጋትን ያካትታል ብለዋል።
▪️ መሪዎቹ የስትራቴጂክ መሳሪያዎች መበራከትን ማስቆም እንደሚያስፈልግ ተወያይተዋል።
▪️ ሁለቱ መሪዎች ኢራን እስራኤልን ማጥፋት በምትችልበት አቋም ላይ በፍፁም መድረስ እንደሌለባት ሃሳብ ተለዋውጠዋል።
@sputnik_ethiopia