የቀድሞው ፈረንሳዊው ኮከብ፣ የአርሰናል እና የማንቸስተር ሲቲ ተጫዋች ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገብቷል።
ባካሪ ሳኛ ኑሮው በዱባይ ሲሆን የኢትዮጵያን እንጀራ በጣም እንደሚወድ ይናገራል።
“በምኖርበት ሀገር ብዙ ኢትዮጵያዊያን አሉ።” የሚለው ሳኛ “ስለኢትዮጵያ ብዙ እንዳውቅ አድርገውኛል ፤ የእኔም የዘር ግንድ ከአፍሪካ መሆኑ በራሱ ስለኢትዮጵያ እንዳውቅ አድርጎኛል።” ነው ያለው።
“የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከግብፅ ጋር ያደረገውን ጨዋታ ተመልክቻለሁ ፤ ኢትዮጵያ ጥሩ ብሔራዊ ቡድን አላት። የዚህ አካል ሆኜ አዲስ አበባ መምጣቴም አስደስቶኛል።”ብሏል።
