ብሔራዊ ባንክ የልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ውጤትን ይፋ ሲያደርግ የዶላር ዋጋ መጠነኛ ቅናሽ አሳይቷል

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ታኅሣሥ 18 ቀን 2018 ዓ.ም. ባከናወነው የዓመት መጨረሻ ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ፣ የአንድ የአሜሪካ ዶላር የጨረታ አማካይ ዋጋ 154.47 የኢትዮጵያ ብር መሆኑን አስታውቋል። 

ባንኩ 150 ሚሊዮን ዶላር ባቀረበበት በዚህ ልዩ ጨረታ ላይ በአጠቃላይ 23 የንግድ ባንኮች ተሳታፊ በመሆን የውጭ ምንዛሬ ማሸነፍ ችለዋል።

ይህ ውጤት ካለፈው የጨረታ አፈጻጸም ጋር ሲነጻጸር  ልዩነት አሳይቷል። ባንኩ ታኅሣሥ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው 12ኛው ዙር ጨረታ የአንድ ዶላር አማካይ ዋጋ 154.7747 ብር ነበረ። ከዛሬው ውጤት ጋር ሲነጻጸር የዶላር ምንዛሬ በ0.19 በመቶ (0.29 ሳንቲም) ገደማ ቅናሽ አሳይቷል። 

50 ሚሊዮን ዶላር በቀረበበት እና ከ 11 ቀን በፊት ብሔራዊ ባንክ ባደረገዉ በዚህ ጨረታ የውጭ ምንዛሬ አግኝተው የነበሩት ባንኮች ቁጥር 13 ብቻ የነበረ ሲሆን፣ በዛሬው ልዩ ጨረታ ግን ቁጥራቸው ወደ 23 ከፍ ብሏል። 

ይህ ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ የተካሄደው የዓመቱን መጠናቀቅ ተከትሎ ሲሆን፣ በገበያው ውስጥ ያለውን የውጭ ምንዛሬ ፍላጎት ለማርካት እና የምንዛሬ ተመኑን ለማረጋጋት ያለመ መሆኑ ተመልክቷል። ባንኩ ቀጣይ ጨረታዎችንም አስቀድሞ በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት እንደሚያከናውን ገልጿል። 

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...