የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት (ብ.ሰ.ማ.ድ) የ2017 በጀት ዓመት በ 6 ወራት ዉስጥ 23.9 ሚሊዮን ካሬ ሜትር ጋዜጦች፣ 27.3 ሚሊዮን ካሬ ሜትር የደህንነት ማተሚያ ውጤቶች እንዲሁም 23.8 ሚሊዮን ካሬ ሜትር የንግድ እና ሌሎች ማተሚያ ውጤቶችን ማሳተሙን አስታዉቋል ።
ድርጅቱ የአቅርቦት ሰንሰለት ተግዳሮቶች ቢኖሩም ከ 578 ሚሊዮን 706 ሺህ ብር በላይ ገቢ ማግኘቱንና በቀጣዮቹ ሁለት ሩብ ዓመታት እና ከዚያ በላይ ምርቱን ለማሳደግ በርካታ አዳዲስ የሥራ ትዕዛዞችን እና የንግድ ሽርክናዎችን አግኝቻለሁ ብሏል።
