ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ በመቄት ወረዳ የመሬት መንሸራተት አደጋ የደረሰበትን ገዳም ጎበኙ

Date:

የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፣ በመቄት ወረዳ በመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት የደረሰበትን የገረገራ ቀራንዮ መድኀኔዓለም አቡነ ተክለሃይማኖትና አባ ሳሙኤል አንድነት ገዳም አዲስ ሕንጻ ቤተክርስቲያን ትናንት ጎብኝተዋል።

ብፁዕነታቸው በአደጋው የተጎዳውን ቤተክርስቲያን ከተዘዋወሩ በኋላ ከወረዳው ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ ከሰበካ ጉባኤ አባላት እና ከሕንጻ አሠሪ ኮሚቴ አባላት ጋር ጥልቅ ውይይት አድርገዋል።

የሕንጻ አሠሪ ኮሚቴው በበኩሉ፣ ቤተክርስቲያኑ የደረሰበትን ጉዳት ተከትሎ በርካታ ወገኖች በገንዘብ፣ በጉልበትና በእውቀት እያደረጉት ያለውን ሁለንተናዊ ድጋፍ አስረድቷል።

በተጨማሪም፣ የከፋ አደጋ እንዳይደርስ ለመከላከል የተከናወኑ ተግባራትን በዝርዝር አብራርተዋል።

ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፣ የቤተክርስቲያኑ ሁኔታ በመገናኛ ብዙኃን ከሚገለጸው በላይ አሳሳቢና አስቸኳይ ትኩረት የሚሻ መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም፣ በሰለጠኑና ልምድ ባላቸው የምህንድስና ባለሙያዎች ድጋፍ፣ ጊዜያዊና በጥናት ላይ የተመሠረተ ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጥ አባታዊ የሥራ መመሪያ አስተላልፈዋል።

ይህ ጉብኝትና የተላለፈው መመሪያ፣ የጥንታዊቷን ገዳም መልሶ ለመገንባትና ተጨማሪ ጉዳት እንዳይደርስ ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ የኢራን የኒውክሌር ተቋም ላይ ጥቃት ለማድረስ ዛቱ

አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርሰው ጥቃት 11ኛ ቀኑን ይዟል። ፕሬዝዳንት...

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአሜሪካ ” American Space ” ማዕከል ተመረቀ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቨን ማሲንጋ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመውን "American...

አሐዱ ባንክ ለ 8ኛ ጊዜ የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናወነ

አሐዱ ባንክ ሥራ የጀመረበትን 4ኛ ዓመት በማስመልከት የተለያዩ ኩነቶችን...

ዕንባ ጠባቂ ከቀረቡለት አቤቱታዎች 84% በመንግስታዊ ተቋማት ላይ የቀረቡ ናቸው

የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በተጠናቀቀው የ2018 በጅት ዓመት...