የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር 70ኛ ዓመትን እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት ምሥረታ የአልማዝ ኢዩቤልዩ በዓልን ምክንያት በማድረግ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያሬድ የሙዚቃ ት/ቤት እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር የስትሪንግ ኦርኬስትራ በጋራ ታላቅ ሲነፎኒ ኦኬስትራ ኮንሰርት አቀረቡ፡፡
ሲንፎኒ ስትሪንግ ኦኬስትራው ካቀረበው ኮንሰርት ውስጥ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መዝሙር ኮንዳክተር ሰለሞን ሉሉ፤” እረኛው ባለዋሽንት” (ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ ፡አክሊሉ ዘውዴ) ‹‹የልቤ ጉዞ›› ኮንዳክተር (አማኑኤል ቡሌ ፤ረዳት ፕሮፌሰር አክሊሉ ዘውዴ) የአስቴር አወቀ ‹‹ጠይም ዘለግ ያለ›› ‹‹ የክቡር ዶ/ር የጥላሁን ገሠሠ ‹‹እንኳን ቆሜ ብቀበርም..›› ኮንዳክተር ዶ/ር ዕዝራ አባተ ‹‹የተነቃቃ ስሜት›› በረዳት ፕሮፌሰር አክሊሉ ዘውዴ የተቀመሩ ሥራዎች የቀረቡ ሲሆን የዕለቱን ሲነፎኒ ኦኬስትራ ኮንሰርት በ ረ/ፕ አክሊሉ ዘውዴ መራሒ ሙዚቃ መሪነት ቀርቧል፡፡
በዕለቱ የሙዚቃ ተመራማሪና ባለሞያ የኢትዮጵያ ቤተመጽሐፍትና ቤተመዛግብት አገልግሎት ዋና ዳይሬክትር አቶ ሰርጸፍሬ ስብሀት እና ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ የሙዚቃ አፍቃሪያን ተገኝተዋል፡፡
