ትራምፕ የኖቤል ሰላም ሽልማት ተበረከተላቸው

Date:

የቬንዙዌላዋ የኒኮላስ ማዱሮ አስተዳደር ተቺና ተቃዋሚ የኖቤል ስላም ሽልማታቸውን ለፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሰጡ።

ማሪያ ኮሪና ማቻዶ “ትራምፕ ለነፃነታችን የተለየ ዋጋ በመክፈላቸው የተከበረውን የኖቤል ሰላም ሽልማት ሰጥቻቸዋለሁ” ሲሉ ምክንያታቸውን አስቀምጠዋል።

የኖቤል ሽልማት ኮሚቴን አሰራር የጣሰ ነው ቢባልም ትራምፕ ሽልማቱ ተበርክቶላቸዋል።

ሽልማቱ ለሌላ አካል ተላልፎ እንደማይሰጥም ኮሚቴው ቀድሞ ማሳሰቡ የሚዘነጋ አይደለም።

ማቻዶ ፕሬዚዳንት ትራምፕን ካገኙ በኋላ በካፒቶል ለጋዜጠኞች ሀሳብ የሰጡ ሲሆን ለካራካስ ነፃነት ሪፐብሊካኑ ዋጋ ከፍለዋል ብለዋል።

በዕርግጥ ትራምፕ በካሪቢያን በኩል የቬንዙዌላን ነዳጃ ወደ አሜሪካ ለማጋዝ ያደረጉት ነው በሚል ይወቀሳሉ።

የኖቤል ሽልማት ከተሰጠ በኋላ ለማንም አሳልፎ መስጠትም ሆነ ማጋራት እንደማይቻል ግልፅ በሆነ መንገድ ቢቀመጥም ማቻዶ አሰራሩን ጥሰው ለትራምፕ ዕውቅና ሰተዋቸዋል።

ማቻዶ የኖቤል ሽልማትን ያገኙት ቬንዙዌላን ከአምባገነናዊ ወደ ዴሞክራሲያዊ መንግስት ለማሻገር ባደረጉት ጥረትና ለነፃነት በከፈሉት ዋጋ ነበር ተብሏል።

ዘ ዋሽንግተን ፖስት

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ይህንዓለም አቅናው የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆኑ

በኢትዮጵያ በፍጥነት እያደጉ ከሚገኙ እና ከፍተኛ የባለአክስዮኖች ቁጥር ካላቸው...

ማዕቀቦች የኢራንን የኒውክሌር መርሃ-ግብር ቢያደናቅፉም መንግስቱን ሊጥሉ እንደማይችሉ ተገለጸ

ማዕቀቦች የኢራንን ወታደራዊ እና የኒውክሌር እንቅስቃሴዎች አስቸጋሪና ውድ እንዲሆኑ...

የአፍሪካ ሀገራት አዲስ የኢንቨስትመንት ፈንድ ይፋ አደረጉ

በአፍሪካ ሀገራት ላይ የተደቀነውን ከፍተኛ የብድር ጫና ለማቃለል እና...

ዶናልድ ትራምፕ “በቅርቡ” ሆርሙዝ የአሜሪካ ግዛት አካል እንደሚሆን ተናገሩ

ከኢራን ጋር ያለው ግጭት እየተባባሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የአሜሪካው...