ከዋሽንግተን ዲሲ እስከ ኒውዮርክ ከቦስተን እስከ ቺካጎ እና ሎስ አንጀለስ ድረስ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰልፈኞች ዋና ዋና ጎዳናዎችን በማጥለቅለቅ በጥር ወር ወደ ሥልጣን በመጡት ትራምፕ ላይ ተቃውሟቸውን በማሰማት ላይ ይገኛሉ።
ሰልፈኞቹ በትራምፕ ላይ ተቃውሞ ለማሰማት ወደ አደባባይ የወጡት ፕሬዝዳንቱ ከማህበራዊ እስከ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በሚያራምዳቸው አጀንዳዎች ደስተኛ ባለመሆናቸው እንደሆነ ሮይተርስ ዘግቧል።
