Nestle የተሰኘው የህፃናት ምግብ አምራች ኩባንያ “SMA, BEBA, NAN እና Alfamino” የተሰኙት የህፃናት ምግቦች ላይ ማቅለሽለሽ እና ማስመለስ የሚያስከትል “cersulide” ከተሰኘ ኬሚካል ጋር የተነካኩ ናቸው በማለት ምርቶቹ እንዲመለሱ ጥሪ አቅርቧል።
ድርጅቱ መጀመሪያ ጥሪውን ያቀረበው በአውሮፓ በሚገኙ አንዳንድ ምርቶች ላይ የነበረ ቢሆንም በኋላ ላይ ጥሪውን ወደ አፍሪካ፣ አሜሪካና እስያ አስፍቷል።
ኩባንያው እስካሁን ከምግቦቹ ጋር በተያያዘ የተፈጠረ የጤና እክል እንደሌለ ቢገልጽም ደቡብ አፍሪካን ጨምሮ 37 ሃገራት ከህፃናት ምግቡ ጋር በተያያዘ የጤና ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
የብራዚል የጤና ሚኒስቴር መርዛማው ነገር የተገኘው በኔዘርላንድስ በተመረቱት ላይ ነው ሲል፣ የኔዘርላንድስ ተቋሙ በስዊዘርላንድ የተመረቱት ላይ ነው ብሏል።
የደቡብ አፍሪካ የጤና ሚኒስትር ወደ ኩባንያው እንዲመለሱ የተጠሩት ምርቶች በባለፈው ሰኔ የተመረቱና የ18 ወራት ቆይታ ያላቸው እንደሆኑ ገልጿል።
ዜናው ከተሰማ በኋላም የህፃናት የምግብ አምራቹ ኩባንያ ነስትል የአክሲዮን ዋጋ በ5.7% ቀንሷል።
Nestle ከዚህ ቀደም ወደ አፍሪካ በሚልካቸው የህፃናት ምግቦች ላይ ከመጠን በላይ ስኳር ይጨምራል ተብሎ ተከሶ ነበር።
ዘገባው የሮይተርስ ነው።
