ከ2007 ዓ.ም. ጀምሮ በየዓመቱ ደራሲያንና አንባቢያንን እያገናኘ ያለው “ንባብለሕይወት” የመጽሐፍት ዐውደ ርዕይ ከዛሬ ሐምሌ 24 ቀን ጀምሮ እስከ እሑድ ሐምሌ 27 ቀን ድረስ ይቆያል።
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጽሐፍት ኤጀንሲ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ እና ሌሎች ተቋማትም የንባብ ለህይወት አካል ናቸው።
በዐውደ ርዕዩ ላይ የልጆች መጽሐፍት፣የታሪክ፣ የፖለቲካ፣ የቢዝነስ (ኢኮኖሚ)፣ ልብወለድ፣ ግጥም፣ የጠፉና አዳዲስ መጽሐፍቶች ጨምሮ በየዘውጉ ይገኛሉ።
ደራሲያንን ማስፈረምና የጋራ ፎቶዎችን መነሳት፣ ከማተሚያ የወጡ አዳዲስ መፅሐፍቶችን በአንባቢያን ማስመረቅ የዐውደ ርዕዩ አካል ናቸው።
