አሊኮ ዳንጎቴ ከዳንጎቴ ሲሚንቶ ሊቀመንበርነት ለቀቁ

Date:

ናይጄሪያዊው ቢሊየነር አሊኮ ዳንጎቴ ከዳንጎቴ ሲሚንቶ ሊቀመንበርነት መልቀቃቸውን ይፋ አድርገዋል።

ይህ ውሳኔ ከዚህ ቀደም ከሌላኛው ድርጅታቸው ከለቀቁ በኋላ የመጣ ሲሆን፣ ኩባንያው የዳንጎቴ መልቀቅ አስቀድሞ ታቅዶ በነበረው የአመራር ሽግግር ሂደት አካል እንደሆነ አስታውቋል።

በአቶ ዳንጎቴ ምትክ ኢማኑኤል ኢካዞቦህ የዳንጎቴ ሲሚንቶ አዲስ ሊቀመንበር ሆነው ተሹመዋል።

ዳንጎቴ ሲሚንቶ በአፍሪካ ትልቁ የሲሚንቶ ፋብሪካ ሲሆን፣ ናይጄሪያን ከሲሚንቶ አስመጪነት ወደ ትልቁ ላኪነት በመቀየር ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል።

ድርጅቱ በዓመት 48.6 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ሲሚንቶ ያመርታል።

በኢትዮጵያ የሚገኘው የዳንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካ በቅርቡ 400 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ የማስፋፊያ ፕሮጀክት እንደሚካሄድበት ተገልጿል።

ይህ መስፋፋት የፋብሪካውን የዓመት ምርት ከ5 ሚሊዮን ቶን በላይ ከማድረጉም በላይ ለተጨማሪ 25,000 ሰዎች የስራ እድል እንደሚፈጥር ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...