በመካከለኛው ምስራቅ በአሜሪካና በኢራን መካከል ያለው ውጥረት በከፍተኛ ሁኔታ በጨመረበት በዚህ ወቅት፣ የአሜሪካ እና የእስራኤል የባሕር ኃይሎች በቀይ ባሕር ላይ የጋራ ወታደራዊ ልምምድ ማድረጋቸውን አስታወቁ።
ተሳታፊ መርከቦች፦ በአሜሪካ በኩል የሚሳኤል ተኳሽ የሆነችው USS Delbert D. Black የተሳተፈች ሲሆን፣ በእስራኤል በኩል ደግሞ INS Eilat የተሰኘችው የጦር መርከብ ተሳትፋለች።
የልምምዱ ዓላማ፦ ሁለቱ አገራት ልምምዱን “መደበኛ” (Routine) ብለው ቢገልጹትም፣ የእስራኤል መከላከያ ኃይል ግን ስምሪቱ በሁለቱ ጦሮች መካከል ያለውን “የጠበቀ ትብብር” የሚያሳይ መሆኑን ገልጿል።
የመርከቧ አቅም፦ በልምምዱ የተሳተፈችው የአሜሪካዋ የጦር መርከብ በአየር፣ በባሕር እና በባሕር ሰርጓጅ መከላከያ የታጠቀች ሲሆን፣ በየብስ ላይ ባሉ ኢላማዎች ላይም ጥቃት የማድረስ ብቃት አላት።
ከጀርባ ያለው ምክንያት፦
ይህ ልምምድ የተካሄደው በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሚመራው የአሜሪካ አስተዳደር በኢራን ላይ ያለውን ጫና በጨመረበት ወቅት ነው። በተለይም በኢራን ውስጥ በተነሳው ተቃውሞ ላይ መንግሥት የወሰደውን እርምጃ ተከትሎ፣ ዋሽንግተን ወታደራዊ እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል በተደጋጋሚ ስታስጠነቅቅ ቆይታለች።
