አሜሪካ ለዩክሬን የምታደርገውን ወታደራዊ ድጋፍ ለጊዜው ማቋረጧን አስታወቀች

Date:

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሀገራቸው ለዩክሬን የምታደርገው ወታደራዊ ድጋፍ በጊዜያዊነት እንዲቋረጥ መወሰናቸው ተገልጿል።

ውሳኔው ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከዩክሬን አቻቸው ቮሎድሚር ዘለንስኪ ጋር ከቀናት በፊት በነጩ ቤተመንግስት ያደረጉት ውይይት ባለመግባባት መቋጨቱን ተከትሎ የተደረሰ ነው።

አሜሪካ ውሳኔውን ያሳለፈችው ለዩክሬን የምታደርገው ድጋፍ መፍትሄ ማምጣት በሚያስችል አግባብ ጥቅም ላይ መዋሉን ለመገምገም እንደሆነ ተጠቅሷል።

በአሜሪካ ውሳኔ ዙሪያ ፕሬዚዳንት ዘለንስኪን ብጠይቅ ምላሽ አጣሁ ያለው የሬውተርስ የማለዳ ዘገባ በዋሽንግተን የዩክሬን ኤምባሲም ዝምታን መምረጡን አስነብቧል።

አሜሪካ ባለፉት ሶስት ዓመታት ለዩክሬን የ175 ቢሊየን ዶላር አጠቃላይ ድጋፍ ማደርጓ ይታወሳል።

አሜሪካ ለዩክሬን የምታደርገውን ወታደራዊ ድጋፍ ለጊዜው ማቋረጧን አስታወቀች

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሀገራቸው ለዩክሬን የምታደርገው ወታደራዊ ድጋፍ በጊዜያዊነት እንዲቋረጥ መወሰናቸው ተገልጿል።

ውሳኔው ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከዩክሬን አቻቸው ቮሎድሚር ዘለንስኪ ጋር ከቀናት በፊት በነጩ ቤተመንግስት ያደረጉት ውይይት ባለመግባባት መቋጨቱን ተከትሎ የተደረሰ ነው።

አሜሪካ ውሳኔውን ያሳለፈችው ለዩክሬን የምታደርገው ድጋፍ መፍትሄ ማምጣት በሚያስችል አግባብ ጥቅም ላይ መዋሉን ለመገምገም እንደሆነ ተጠቅሷል።

በአሜሪካ ውሳኔ ዙሪያ ፕሬዚዳንት ዘለንስኪን ብጠይቅ ምላሽ አጣሁ ያለው የሬውተርስ የማለዳ ዘገባ በዋሽንግተን የዩክሬን ኤምባሲም ዝምታን መምረጡን አስነብቧል።

አሜሪካ ባለፉት ሶስት ዓመታት ለዩክሬን የ175 ቢሊየን ዶላር አጠቃላይ ድጋፍ ማደርጓ ይታወሳል።

ቀዳሚ ጽሑፍ
ቀጣይ ጥሑፍ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...