አሜሪካ በመካከለኛው ምስራቅ ለሚገኙ ዜጎቿ አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ አስተላለፈች

Date:

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ አዳዲስ ወታደራዊ ጥቃቶች ሊሰነዘሩ እንደሚችሉ ካስጠነቀቁ በኋላ፣ አሜሪካ በመካከለኛው ምስራቅ የሚኖሩ ዜጎቿ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉና አስፈላጊ ከሆነም አካባቢውን በፍጥነት ለመልቀቅ ዝግጁ እንዲሆኑ አሳሰበች።
 
በነዚህ ቀናት በባህሬን፣ ኢራቅ፣ እስራኤል፣ ዮርዳኖስ፣ ኩዌት፣ ሊባኖስ፣ ኦማን፣ ኳታር፣ ሳዑዲ ዓረቢያ እና የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ የሚገኙ የአሜሪካ ኤምባሲዎች በሙሉ ለዜጎቻቸው በላኩት የጥንቃቄ መልእክት፤ ድንገተኛ የበረራ መሰረዞች፣ የአየር ክልል መዘጋቶች እና የጉዞ መስተጓጎሎች ሊያጋጥሙ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል።
 
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በሰጡት አስተያየት ዲፕሎማሲያዊ ንግግሮቹ ውጤት ካላመጡ ዋሽንግተን በኢራን ላይ «አደገኛ ጥቃት» ልትሰነዝር እንደምትችል ቢናገሩም፣ ውይይቱ በመቀጠሉ ምክንያት ግን የታሰቡት ጥቃቶች ለጊዜው መገታታቸውን አብራርተዋል።
 
በሌላ በኩል ቴህራን በበኩሏ፤ ከአሜሪካም ሆነ ከእስራኤል ለሚሰነዘርብኝ ማንኛውም ጥቃት ወዲያውኑ ምላሽ እሰጣለሁ ስትል ዝታለች። አክላም ጥቃት ከተፈጸመባት በቀጣናው የሚገኙ የኃይልና የኢነርጂ መሰረተ ልማቶች ላይ ጥቃት እንደምታደርስ  አስጠነቅቃለች።
 
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ውጥረት እየረገበ ካልመጣ ዲፕሎማሲያዊ ተቋማት እና ከአሜሪካ ጋር ቁራኝነት ያላቸው ድርጅቶች ኢላማ ሊሆኑ እንደሚችሉ የገለጸችው አሜሪካ፣ ዜጎቿ ወደ አካባቢው የሚያደርጉትን ጉዞ ድጋሚ እንዲያሰላስሉበት አጥብቃ አሳስባለች።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...