አሜሪካ በቬንዙዌላ ላይ የምታደርሰው ጫና እንዲሁም የመውጣትና መግባት ገደብ የመጣል አካሄድ ህገ ወጥ ነው በሚል የመንግስታቱ ድርጅት ባለሙያዎች ከሰሱ።
ህገ ወጥ ወታደራዊ እርምጃ ነው በሚል አራት የድርጅቱ ባለሙያዎች ወቅሰዋል።
የአሜሪካ ኮንግረስ በጉዳዩ ላይ ጣልቃ እንዲገባም ጠይቀዋል።
አንድን አገር በጦር ዘግቶ አንድ ወገናዊ ማዕቀብ መጣል መብት እንዳልሆነም አሳስበዋል።
ባለሙያዎቹ በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫቸው ተቀባይነት የሌለው ድርጊት ነው በሚል አውግዘዋል፤ጣልቃ ሊገባበት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
አሜሪካ ጦሯን በካሪቢያን እና ፓስፊክ ውቅያኖስ በማስፈር የቬንዙዌላ መንግስት ላይ ጫና እየፈጠረች ነው።
አንድን አገር እንዳይወጣና እንዳይገባ መዝጋት በመንግስታቱ ድርጅት ቻርተር የተከለከለ ነውም ተብሏል።
የጠቅላላ ጉባዔው የ1974 ትርጓሜም ህገ ወጥ ተግባር ነው በሚል ደንግጓል።
አሜሪካ የኒኮላስ ማዱሮ መንግስት
በህገ ወጥ የአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ስራ ላይ ተሰማርቷል በሚል በዓለም አቀፉ የውሀ አካል ላይ ጥቃት መሰንዘር ከጀመረች አራት ወራት ሆኗታል።
አልጀዚራ እንዳስነበበው።
