አበዳሪ ሀገራት የኢትዮጵያን የዩሮ ቦንድ ስምምነት ውድቅ አደረጉት

Date:

ኢትዮጵያ ከግል የቦንድ ባለቤቶች ጋር ደርሳው የነበረው በመርህ ደረጃ ላይ የተመሰረተ ስምምነት (AIP) በዋና አበዳሪ ሀገራት (OCC) ውድቅ ተደርጓል።

ቻይና እና ፈረንሳይ የሚመሩት የሁለትዮሽ አበዳሪዎች ኮሚቴ (OCC) ስምምነቱን ከመረመረ በኋላ ውድቅ ማድረጉ ነው የተገለጸው። ይህ ውሳኔ ሀገሪቱን የአንድ ቢሊዮን ዶላር የዩሮ ቦንድ ዕዳ ለመክፈል እያደረገች ያለችውን ጥረት ወደ ኋላ የሚመልስ ነው።

ለዚህም በምክንያት የተቀመጠው አበዳሪ ሀገራቱ ኢትዮጵያ ከከግል የቦንድ ባለቤቶች ጋር ያደረገችው በመርህ ደረጃ ላይ የተመሰረተ ስምምነት (AIP) “ከእኛ ጋር ሲነፃፀር ፍትሃዊ ያልሆነና የግል ባለሀብቶቹን የጠቀመ ነው” በማለታቸው መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ኮሚቴው ለገንዘብ ሚኒስቴር በላከውና በሚኒስቴሩ በኩል ይፋ በሆነው ደብዳቤ ላይ እንደሰፈረው ስምምነቱ፥ የአበዳሪዎች ኮሚቴ (OCC) እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የሚከተሉትን የአበዳሪዎች እኩልነት መርህ እንዳልተከተለ ይጠቅሳል።

አክሎም፥ “አሁን ባለው ተስፋ ሰጪ የኢኮኖሚ ሁኔታ አንጻር ሲታይ፣ የግል ባለሀብቶቹ ያደረጉት የዕዳ ማሻሻያ ጥረት በጣም አነስተኛ ነው” ሲል ነው የገለጸው።

በተጨማሪም፥ በስምምነቱ ውስጥ የተካተተውና ኢትዮጵያ ወደፊት ኢኮኖሚዋ ሲያድግ ለባለሀብቶቹ ተጨማሪ ክፍያ እንድትፈጽም የሚጠቅሰውንም ክፍል “የዕዳ ሽግሽጉን ሂደት ውስብስብ ከማድረጉም በላይ፣ በአበዳሪዎች መካከል ከፍተኛ የሆነ የጥቅም ልዩነት እንዲፈጠር ያደርጋል ሲል አንስቷል።

የኢትዮጵያ የገንዘብ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መግለጫም ሂደቱ ወደ ኋላ መመለሱ የሚያስቆጭ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ ግን አሁንም ለሰላማዊና ለፍትሃዊ ድርድር ዝግጁ ነች ሲል ገልጿል።

ኢትዮጵያ ይህንን የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮ ቦንድ ብድር የወሰደችው እ.ኤ.አ. በ2014 ሲሆን፣ ብድሩ ለ10 ዓመታት የሚቆይና በየዓመቱ 6.625 በመቶ ወለድ የሚከፈልበት ነበር።

|@tikvahethmagazine

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ የኢራን የኒውክሌር ተቋም ላይ ጥቃት ለማድረስ ዛቱ

አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርሰው ጥቃት 11ኛ ቀኑን ይዟል። ፕሬዝዳንት...

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአሜሪካ ” American Space ” ማዕከል ተመረቀ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቨን ማሲንጋ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመውን "American...

አሐዱ ባንክ ለ 8ኛ ጊዜ የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናወነ

አሐዱ ባንክ ሥራ የጀመረበትን 4ኛ ዓመት በማስመልከት የተለያዩ ኩነቶችን...

ዕንባ ጠባቂ ከቀረቡለት አቤቱታዎች 84% በመንግስታዊ ተቋማት ላይ የቀረቡ ናቸው

የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በተጠናቀቀው የ2018 በጅት ዓመት...