አቢሲንያ ባንክ ከ349 ነጥብ 9 ሚሊየን ዶላር በላይ ብድር አቀረበ

Date:

አቢሲንያ ባንክ የውጭ ምንዛሪ እጥረትን ለመፍታትና የገቢ ንግድን ለመደገፍ በበጀት  ዓመቱ 349 ሚሊየን 943 ሺህ 588 የአሜሪካ ዶላር ብድር ማቅረቡን አስታወቀ፡፡

ባንኩ ለደንበኞች ካቀረበው የምንዛሪ ድልድል ውስጥ በ3ኛው ሩብ ዓመት ከ1 ሺህ በላይ ደንበኞች ወደ ሀገር ውስጥ የገበያ ዕቃዎችን እንዲያስገቡ 189 ሚሊየን 82 ሺህ 861 ዶላር እንዲያገኙ ማድረጉንም ገልጿል፡፡

ይህም የደንበኞችን ፍላጎት ለማሟላት እያደረገ ያለውን ከፍተኛ ጥረት እንደሚያሳይ ነው የገለጸው፡፡

በቀጣይም የውጭ ምንዛሪ ሀብትን በአግባቡ በማሥተዳደር እና ከሀገራዊ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ጋር በማጣጣም የደንበኞቹን ፍላጎት ለሟሟላት እንደሚሠራ አረጋግጧል፡፡

በውጭ ምንዛሪ ድልድል ረገድ በኃላፊነት በመሥራት ለተረጋጋ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት እያበረከተ ያለውን አስተዋፅዖም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁሟል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሎዛ ዘፀአት”እና “የሎዛ ድርሳናት”ተከታታይ ረጅም ልቦለድ መጻሕፍት ተመረቁ

በጋዜጠኛና ደራሲ መርዕድ እስጢፋኖስ የተጻፉት ሎዛ ዘፀአት(2014 ዓ.ም) እና...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!! በክርስቲያኖች ዘንድ ጥምቀት...

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት...

በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም ዓይናቸው በጽኑ መታመሙን ጠበቃቸው ገለጹ

ከሁለት ዓመት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም አበራ...