በዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የአፍሪካ መምሪያ ዳይሬክተር የሆኑት ኢትዮጵያዊው አቶ አበበ አእምሮ ስላሴ፣ ከግንቦት ጀምሮ ኃላፊነታቸውን እንደሚለቁ ተገልጿል።
አቶ አበበ ድርጅቱን በፈረንጆቹ 1994 የተቀላቀሉ ሲሆን፣ ላለፉት 32 ዓመታት በተለያዩ ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎች አገልግለዋል።
ከ2016 ጀምሮ የድርጅቱ ደግሞ የአፍሪካ መምሪያ ዳይሬክተር በመሆን ሰርተዋል።
በቆይታቸውም አፍሪካ በኮቪድ-19 እና በኢኮኖሚ ቀውስ ወቅት የነበሩባትን ፈተናዎች እንድትወጣ ረድተዋል።
በተለይም ለሰሃራ በታች አፍሪካ የሚሰጠውን ድጋፍ በማሳደግና በቦርዱ ውስጥ የአህጉሪቱ ድምፅ እንዲጎለብት በማድረግ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።
የIMF ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂየቫ፤ አቶ አበበ ላሳዩት ጥንካሬ፣ ስትራቴጂካዊ አመራርና ለድርጅቱ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
