የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሁን ላይ በሀገራቱ ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ወደ ቤይሩት እና ቴልአቪቭ የሚያደርገውን በረራ በጊዜያዊነት ማቋረጡን አስታውቋል፡፡ በዚሁ መሠረት አየር መንገዱ ማምሻውን በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባጋራው መረጃ እንዳስታወቀው ወደ ቴልአቪቭ የማደርገውን በረራ እስከ ጥቅምት 7 ቀን አቋርጫለሁ ብሏል፡፡ እንዲሁም ወደ ቤይሩት የሚያደርገውን በረራ ላልተወሰነ ጊዜ ማቋረጡን ገልጾ÷ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ስለሚኖሩ አዳዲስ ጉዳዮች ወደፊት እንደሚያሳውቅ አመላክቷል፡፡
