አየር መንገዱ 362 ሚሊዮን ብር ለመንግሥት እንዲከፍል በኦዲት ተወሰነበት

Date:

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ለአፍሮ ጽዮን ኮንስትራክሽን ኩባንያ በሰጠው የግንባታ ውል መሠረት 1ሺህ 992 መኖሪያ ቤቶች ለመገንባት ከቀረጥ ነፃ መብት የገቡ የግንባታ ዕቃዎች፣ በተለያዩ መንገዶች ያላግባብ ጥቅም ላይ መዋላቸው በጉምሩክ ኮሚሽን ኦዲት በመረጋገጡ 362 ሚሊዮን ብር እንዲከፍል እንደተወሰነበት ተዘገበ።

በውሳኔው ላይ አየር መንገዱ ቅሬታ አቅርቦ እንዲሻር ማድረጉንና ሕገወጥ ድርጊቱን ፈጽመዋል ባላቸው አካላት ላይ ክስ መሥርቶ በክርክር ሒደት ላይ መሆኑን ሪፖርተር ዘግቧል።

የጉምሩክ ኮሚሽን ታኅሳስ 27 ቀን 2016 ዓ.ም. ለአየር መንገዱ በላከው የኦዲት ውጤት ማሳወቂያ ደብዳቤ በአፍሮ ጽዮን ኮንስትራክሽን ኩባንያና በኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ መካከል እ.ኤ.አ. ሐምሌ 17 ቀን 2015 የሠራተኞች መኖሪያ ቤቶች ለመገንባትና የግንባታ ዕቃዎች ከቀረጥ ነፃ መብት አማካይነት ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡ ውል መፈጸሙን አስታውሷል።

ጉምሩክ ኮሚሽን የኦዲት ውጤት ማሳወቂያ እንደሚለው፣ በአየር መንገዱ ስም ከቀረጥና ታክስ ነፃ የገቡ የግንባታ ዕቃዎች “ያላግባብ ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን በመጥቀስ፣ ተገቢው ዕርምጃ እንዲወሰድ በሚል ለኮሚሽናችን ነሐሴ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በጻፈው ደብዳቤ በሰጠው ጥቆማ መሠረት” የምርመራ መስክ ውስን ኦዲት እንዲከናወን ተደርጓል።

ይሁንና አየር መንገዱ ለጉምሩክ ኮሚሽን ባያስገባው ደብዳቤ፣ ከሠራተኞች የመኖሪያ ቤት ግንባታ ፕሮጀክት ሳይት ቀረጥ ያልተከፈለባቸው ዕቃዎች ያላግባብ እየተወሰዱ መሆኑን ገልጾ፣ ንብረቶቹ ከተወሰዱበት እንዲመለሱ አቤቱታ ማቅረቡን ገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!! በክርስቲያኖች ዘንድ ጥምቀት...

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት...

በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም ዓይናቸው በጽኑ መታመሙን ጠበቃቸው ገለጹ

ከሁለት ዓመት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም አበራ...

ንግድ ባንክ “ስታርፔይ” የተሰኘ አዲስ መተግበሪያ ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንክ ሥርዓቱን ይበልጥ ዘመናዊና ቀልጣፋ...