አዲስ አበባ የአፍሪካ የሎጂስቲክስ ማኅበር ዋና መቀመጫ ሆና ተመረጠች

Date:

በቱርክ ኢስታንቡል እየተካሄደ በሚገኘው የአፍሪካ የሎጂስቲክስ ማኅበራት ጉባኤ፥ አዲስ አበባ ከተማን የማኅበሩ ዋና መቀመጫ አድርጎ መምረጡ ተገለጸ።

ይህን የገለጹት ኢትዮጵያን ወክለው በጉባኤው ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የኢትዮጵያ የዕቃ አስተላላፊዎችና የመርከብ ወኪሎች ማኅበር አቶ ዳዊት ውብሸት ናቸው።

በቱርክ እየተካሄደ በሚገኘው ጉባኤ ላይ 35 ሀገራት ተሳታፊ መሆናቸውን የገለጹት አቶ ዳዊት ውብሸት፥ ኢትዮጵያ የቦርድ ወንበር ማግኘቷንም ይፋ አድርገዋል።

የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ይህን ያስታወቁት የሎጂስቲክስ እና ትራንስፖርት ዘርፍ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እና የዩኒቨርሲቲዎች የጋራ የምክክር መድረክ እየተከናወነ በሚገኝበት መድረክ ላይ በቪዲዮ ባስተላለፉት መልዕክት ነው።

ኢትዮጵያ በ2027 የሚካሄደውን የዓለም የእቃ አስተላላፊዎችና የመርከብ ወኪሎች ማህበር (ፊያታ) ጠቅላላ ጉባኤን በመዲናዋ አዲስ አበባ እንደምታስተናግድም ተገልጿል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...