የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በቅርቡ የጸደቀውን የኤችአይቪ መከላከያ መድኃኒት “ሌናካፓቪር” (Lenacapavir) ኤችአይቪን ለመዋጋት በሚደረገው ጥረት ውስጥ አገሮች እንደ መሳሪያ እንዲጠቀሙበት ምክረ ሃሳብ ማቅረቡን ሲኤንኤን (CNN) ዘግቧል።
ይህ መድኃኒት በተለይም ለቫይረሱ ተጋላጭ ለሆኑ ቡድኖች እና የኤችአይቪ ስርጭት ከፍተኛ በሆነባቸው አካባቢዎች ቅድሚያ እንዲሰጠው ተመላክቷል።
የዓለም ጤና ድርጅት ይህንን አዲስ መድኃኒት በይፋ እውቅና ሰጥቶ በተግባር ላይ እንዲውል ማረጋገጫ ቢሰጥም፣ መድኃኒቱ ወደ አፍሪካ እና ሌሎች ታዳጊ አገራት የሚደርስበት ጊዜ እስካሁን ግልጽ አለመሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ አዲስ መድኃኒት የኤችአይቪ ስርጭትን ለመግታት በሚደረገው ዓለም አቀፍ ጥረት ውስጥ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል።
የዓለም ጤና ድርጅት የሰጠው ምክረ ሃሳብ አገራት የቫይረሱን ስርጭት ለመቀነስ የሚጠቀሙባቸውን የመከላከያ ዘዴዎች ለማስፋት ይረዳል።
