አድማስ ዩኒቨርስቲ ከ6ሺህ በላይ ተማሪዎች አስመረቀ

Date:

አድማስ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ6ሺህ በላይ ተማሪዎች በሚሊኒየም አዳራሽ አስመርቋል።

በምረቃ ሥነሥርዓቱ ለይ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቱው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሞላ ፀጋዬ ፤ ዩኒቨርስቲው ባለፉት 26ዓመታት በመደበኛና  በርቀት ትምህርት በድግሪ ፣በዲፕሎማና በሰርተፍኬት በርካታ ተማሪዎችን  በማሰልጠን ማስመረቁን  ተናግረዋል ።

ዩኒቨርሲቲው በሃገሪቱ የልማት እንቅስቃሴ ውስጥ የሚፈለገው የተማረ  የሰው ሃይል አሰልጥኖ በማቅረብ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል ።

በዛሬው እለት ከ6 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ያስመረቀው አድማስ ዩኒቨርሲቲ  ካስመረቃቸው  ተማሪዎች  መካከል 71 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል ።

አድማስ ዩኒቨርስቲ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ በሶማሌላንድና ፑንትላንድ ቅርንጫፍ ከፍቶ እያስተማረ እንደሚገኝ ተጠቁሟል።

ተመራቂ  ተማሪዎች በሠለጠኑበት የሞያ መስክ ሀገራቸውንና ህዝባቸውን በታማኝነትና በቅንነት ማገልገል እንዳለባቸው መልዕክት ተላልፏል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...