አፍሪካውያን መሪዎች እና ምሁራን ለጣና ፎረም ወደ ባሕር ዳር እየገቡ ነው

Date:

ጣና ፎረም በአፍሪካ የደኅንነት ጉዳዮች ዙሪያ የአሕጉሪቷ መሪዎች እና ምሁራን የታላቁ የጣና ሐይቅ መገኛ በኾነው ባሕር ዳር ከተማ ከትመው የሚወያዩበት ከፍተኛ ፎረም ነው።

ፎረሙ ጥቅምት 14/2018 ዓ.ም ጀምሮ 11ኛ ፎረሙን በባሕር ዳር እና አዲስ አበባ ከተማ ያካሂዳል።

ባለዘንባባዋ ከተማም ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት በመግባት ላይ የሚገኙ እንግዶቿን ከዋዜማው ጀምራ እየተቀበለች ነው።

የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ መሪዎች እና የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር የሥራ ኀላፊዎች በባሕርዳር ደጅአዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተገኝተው እንግዶችን እየተቀበሉ ይገኛሉ።

የአፍሪካውያን እንግዶች የባሕር ዳር ከተማ ቆይታ ያማረ ይኾን ዘንድ አሥፈላጊው ዝግጅት እንደተደረገም ታውቋል። መረጃው የክልሉ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...