ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ የኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።
መሪዎቹ በቁልፍ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ምክክር አድርገዋል። በኢንቨስትመንት እና በሀብት አስተዳደር የቴክኒክ ትብብር ለማድረግ የመግባቢያ ስምምነት ተፈርሟል።
ሁለት ግዙፍ የኃይል ማስተላለፊያ ፕሮጀክቶችን ወደ ተግባር የሚያስገቡ የልማት ስምምነቶች የተፈረሙ ሲሆን የሁርሶ-አይሻ (400 ኪሎ ቮልት) እና የደገሃቡር-ቀብሪደሃር (132 ኪሎ ቮልት) ፕሮጀክቶች ናቸው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እነዚህ ስምምነቶች በሀገራቱ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር እና ስትራቴጂካዊ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት ረገድ ትልቅ እርምጃ መሆናቸውን ገልጸዋል።
