ኢትዮጵያ ሀሴትን ወከለች

Date:

(MISS WORLD ETHIOPIA) በመባል የሚዘጋጀውን አለም አቀፍ የቁንጅና ውድድር ሞዴል ሀሴት ደረጀ በሚካኒካል ኢንጅነሪንግ ሁለተኛ አመት የአዲስ አበባ ሳይንስና ዩንቨርስቲ ቲክኖሎጂ ተማሪ የሆነችውን አንደኛ በመውጣት ህንድ አገር የሚዘጋጀውን ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያን በመወከል የምትወዳደር ይሆናል፡፡

በዚህ ውድድር ላይ ከ110 ሀገራት በላይ የሚሳተፉበት የቁንጅና ውድድር ሲሆን ይህ ውድድር የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ ለማስተዋወቅ መንግስት እየሰራበት የሚገኘውን ስራ ከማስታዋወቁም አንፃር የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ ለውጩ አለም ለማስተዋወቅ የሚረዳ ትልቅ መድረክ ነው፡፡

በዚህ የቁንጅና ውድድር ላይ ተወዳዳሪዋ በአንድ ወር በህንድ አገር ቆይታዋ ድምጽ ለመስጠት የተለያዩ ቦታ ያሉ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ድምፅ እንዲሰጧት እና ውድድሩን ለማሸነፍ የራሱ አስተዋጽኦ ስለሚኖረው ሁሉም ሰው አለም አቀፍ የሆነውን የሚስ ወርልድ ድረ ገፃችን በመግባት ኢትዮጵያን የወከለችዋን ሞዲል ሀሴትን ደረጀን ድምፅ እንዲሰጣት በአክብሮት የምንጠይቅ ይሆናል፡፡

ሊንኩንም አያይዘንላችኋል
ይህ ውድድር እንዲዘጋጅ ትልቁን አስተዋፆ ያረገው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ትልቅ ምስጋና እንሰጣለን፡፡

ይህን አለማቀፍ የቁንጅና ውድድር ከ2014 እስከ 2024 እ.ኤ.አ ኢትዮጵያ ቢውቲ ኩዊንስ እና ፓሽን ፕሮሞሽን እና ኢቨንት ኃ/የተ/የግ/ማህበር በጋራ ያዘጋጁት ሲሆን ዘንድሮም 2025 በቅርቡ እንደሚያዘጋጁ አዘጋጆቹ ገልፀውልናል፡፡

ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ ሁላችንም እንምረጥ!!!

https://www.missworld.com/news/miss-world-ethiopia-2024

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ የኢራን የኒውክሌር ተቋም ላይ ጥቃት ለማድረስ ዛቱ

አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርሰው ጥቃት 11ኛ ቀኑን ይዟል። ፕሬዝዳንት...

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአሜሪካ ” American Space ” ማዕከል ተመረቀ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቨን ማሲንጋ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመውን "American...

አሐዱ ባንክ ለ 8ኛ ጊዜ የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናወነ

አሐዱ ባንክ ሥራ የጀመረበትን 4ኛ ዓመት በማስመልከት የተለያዩ ኩነቶችን...

ዕንባ ጠባቂ ከቀረቡለት አቤቱታዎች 84% በመንግስታዊ ተቋማት ላይ የቀረቡ ናቸው

የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በተጠናቀቀው የ2018 በጅት ዓመት...