የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት እስከ 1.2 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ናፍጣ እና እስከ 650,000 ሜትሪክ ቶን መደበኛ ነዳጅ አቅርቦት የሚውል ዓለም አቀፍ ጨረታ አውጥቷል።
በዚህ ጨረታ ላይ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ኩባንያዎች ከ1.6 ቢሊዮን ብር በላይ የጨረታ ማስከበሪያ ገንዘብ (Bid security) ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
ተጫራቾች እስከ ሚያዚያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ የመወዳደሪያ ሰነዶቻቸውን ማቅረብ እንደሚችሉ ተገልጿል ።
