ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ውስጥ ከኒውክሌር ኃይል ኢነርጂ ማመንጨት እንደምትጀምር ተገለፀ

Date:

የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኃይል ኮሚሽን፣ ሃገሪቱ የኒውክሌር ኃይል ልማት መሠረተ ልማቶችን እያዘጋጀች መሆኑንና በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት እንደምትጀምር አስታወቀ።

የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር አብዱራዛቅ ኡመር እንደገለጹት፤ የኒውክሌር ኃይል ልማት ፕሮግራሞችን አከናውኖ ኃይል ማመንጨት ከ10 እስከ 15 ዓመታት ሊፈጅ ቢችልም፣ ኢትዮጵያ እያከናወነች ባለው የቅድመ ዝግጅት ሥራ ግን በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ውስጥ ኃይል ማመንጨት ትጀምራለች ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል።

አክለውም ለሥራው የሚያስፈልጉ ተቋማት መደራጀታቸውን፣ አስፈላጊ የሆኑ መሠረተ ልማቶች እየተገነቡ መሆኑንና የደኅንነት ጥንቃቄ ሥራዎችም በመከናወን ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል።

የኒውክሌር ልማት ፕሮግራሙ የኃይል አቅርቦትን ከአየር ንብረት ጋር በተጣጣመ መልኩ አስተማማኝ ለማድረግ ያለመ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በተጨማሪም ቴክኖሎጂው በጤና፣ በኢንዱስትሪና በግብርና ዘርፎች ምርታማነትን ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸው፤ ኒውክሌር ኃይልን ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለልማት ለማዋል ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ በመሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር መጀመሩን መናገራቸውን ኢፕድ ዘግቧል።

ቀደም ሲል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምረቃ ሥነ-ሥርዓት ወቅት ኢትዮጵያ የኒውክሌር ኃይል ልማት ፕሮግራም እንደምትጀምር ማስታወቃቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ይህን ተከትሎም የሚኒስትሮች ምክር ቤት ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኃይል ኮሚሽን እንዲቋቋም መወሰኑና የሚመራበት አዋጅም ይፋ መደረጉ አይዘነጋም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...