ኢትዮጵያ እና ፓኪስታን የንግድ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ጅቡቲን የሚያካትት ባለሦስትዮሽ የባህር ላይ ጥምረት ለመመስረት ተስማምተዋል።
ይህም ኢትዮጵያ የጅቡቲን ወደብ በብቃት በመጠቀም ከእስያ ሀገራት ጋር የምታደርገውን የንግድ ልውውጥ ለማሳደግ ይረዳታል። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ከፓኪስታን መድሃኒቶችን፣ አልባሳትን፣ ማዳበሪያን እና ሩዝን ጨምሮ በርካታ ምርቶችን እያስመጣች ሲሆን፣
ይህ አዲስ ስምምነት የሁለቱን ሀገራት የኢኮኖሚ ትስስር ይበልጥ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
