ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላትን አቅም ለአለም ለማሳየት እና የአፍሪካ የቴክኖሎጂ ማዕከል ለመሆን የሚያስችላትን ጉዞ ያጠናክራል የተባዉ አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ (ETEX 2025) በአዲስ አበባ ልታዘጋጅ መሆኑ ተገለፀ።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት (EAll) በጋራ የሚያዘጋጁት ይህ ኤክስፖ ከ100 በላይ የሀገር ውስጥና አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ድርጅቶች፣ ከ50 በላይ ስታርታፖች እንዲሁም ከ10 ሺህ በላይ ሰዎች የሚሳተፉበት ነው።
ከግንቦት 8 እስከ 10 ፤2017 ዓ.ም. በሚካሄደዉ ኤክስፖው ላይ የቴክኖሎጂ ውጤቶችና አገልግሎቶች የሚቀርቡበት ዓውደ ርዕይ፣ ወርክሾፖች፣ ጥናታዊ ወረቀቶች፣ የፓናል ውይይቶች፣ የሃካቶን እና የ AI ሮቦቲክስ ውድድሮች እንደሚቀርብ ካፒታል ሰምቷል።
ኤክስፖው በሳይበር ደህንነት፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት(Al)፣ ፋይናንስ ቴክኖሎጂ (FinTech)፣ ስማርት ከተማ (Smart City)፣ እንዲሁም በቴክኖሎጂ ትምህርት (Tech Education) ላይ እንደሚያተኩር ተነግሯል።
CapitalNews
