ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖን ልታዘጋጅ ነው

Date:

ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላትን አቅም ለአለም ለማሳየት እና የአፍሪካ የቴክኖሎጂ ማዕከል ለመሆን የሚያስችላትን ጉዞ ያጠናክራል የተባዉ አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ (ETEX 2025) በአዲስ አበባ  ልታዘጋጅ መሆኑ ተገለፀ።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት (EAll) በጋራ የሚያዘጋጁት ይህ ኤክስፖ ከ100 በላይ የሀገር ውስጥና አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ድርጅቶች፣ ከ50 በላይ ስታርታፖች እንዲሁም ከ10 ሺህ በላይ ሰዎች የሚሳተፉበት ነው።

ከግንቦት 8 እስከ 10 ፤2017 ዓ.ም. በሚካሄደዉ ኤክስፖው ላይ የቴክኖሎጂ ውጤቶችና አገልግሎቶች የሚቀርቡበት ዓውደ ርዕይ፣ ወርክሾፖች፣ ጥናታዊ ወረቀቶች፣ የፓናል ውይይቶች፣ የሃካቶን እና የ AI ሮቦቲክስ ውድድሮች እንደሚቀርብ ካፒታል ሰምቷል።

ኤክስፖው በሳይበር ደህንነት፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት(Al)፣ ፋይናንስ ቴክኖሎጂ (FinTech)፣ ስማርት ከተማ (Smart City)፣ እንዲሁም በቴክኖሎጂ ትምህርት (Tech Education) ላይ እንደሚያተኩር ተነግሯል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...