ኢትዮጵያ የሕዳሴው ግድብ የግጭት ምንጭ ሊሆን እንደማይችል ገለጸች

Date:

ኢትዮጵያ በሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ከግብፅ ጋር ጦርነት ውስጥ ትገበላች መባሉን ውድቅ ማድረጓን ስፑትኒክ ዘግቧል፡፡

በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 6ኛው የፓን አፍሪካ ፓርላማ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያን የወከለው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የፓን አፍሪካ ቡድን፣ የግጭት መከላከል ቅድመ ማስጠንቀቂያ የአቻ ግምገማ ላይ በአንድ ጽሑፍ አቅራቢ ለተነሳው ሐሳብ  ምላሽ ሰጥቷል፡፡

ኢትዮጵያና ግብፅ ድንበር እንደማይጋሩ የሞገቱት የልዑኩ አባል ዶ/ር  አወቀ አምዛዬ፤ በሁለቱ ሀገራት መካከል ምንም ዓይነት የድንበር ግጭት እንደሌለና ግድቡም የግጭት ምንጭ ሊሆን እንደማይችል አበክረው ገልጸዋል።

“ግጭት እንዲፈጠር ምክንያት ሊሆኑ የሚችሉት ኢትዮጵያን አግልሎ የአባይን ውሃ የመጠቀም ሙሉ መብት ግብፅ እንድትጎናፀፍ የሚያደርጉ በብሪታንያ፣ ግብፅና ሱዳን መካከል የተደረጉ ጊዜ ያለፈባቸው የቅኝ ግዛት ዘመን ስምምነቶች ናቸው” ብለዋል። 

የአፍሪካ ኅብረትና የፓን አፍሪካ ፓርላማ እነኚህ የቅኝ ግዛት ስምምነቶች ሙሉ በሙሉ እንዲሰረዙ ብርቱ ጥረት ማድረግ እንዳለባቸውም ዶ/ር አወቀ አምባዬ  አሳስበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...