በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር በመሆን ያገለገሉት ኤልሳቤጥ ወልደጊዮርጊስ(ዶ/ር) ከዚህ አለም በሞት ተለዩ፡፡
በኮኔል ዩኒቨርሲቲ እና በኒውዮርክ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ ትምህርታቸውን የተከታተሉት ዶ/ር ኤልሳቤጥ በሸገር ሬዲዮ በ #ሸገር_ካፌ ፕሮግራም በሥነ ጥበብና ታሪክ ጉዳዮች ላይ በተደጋጋሚ በመቅረብ እውቀታቸውን አካፍለዋል፡፡
ለስራ ከቆዩበት በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ሻርጃ ከተማ ማረፋቸው ተሰምቷል፡፡
የዶ/ር ኤልሳቤጥ አስከሬን ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ሰምተናል፡፡
ለዶ/ር ኤልሳቤጥ ወልደጊዮርጊስ ወዳጅ ዘመዶች ሸገር መፅናናትን ይመኛል፡፡
