ኤልሳቤጥ ወልደጊዮርጊስ (ዶ/ር) ከዚህ አለም በሞት ተለዩ

Date:

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር በመሆን ያገለገሉት ኤልሳቤጥ ወልደጊዮርጊስ(ዶ/ር) ከዚህ አለም በሞት ተለዩ፡፡

በኮኔል ዩኒቨርሲቲ እና በኒውዮርክ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ ትምህርታቸውን የተከታተሉት ዶ/ር ኤልሳቤጥ በሸገር ሬዲዮ በ #ሸገር_ካፌ ፕሮግራም በሥነ ጥበብና ታሪክ ጉዳዮች ላይ በተደጋጋሚ በመቅረብ እውቀታቸውን አካፍለዋል፡፡

ለስራ ከቆዩበት በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ሻርጃ ከተማ ማረፋቸው ተሰምቷል፡፡

የዶ/ር ኤልሳቤጥ አስከሬን ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ሰምተናል፡፡

ለዶ/ር ኤልሳቤጥ ወልደጊዮርጊስ ወዳጅ ዘመዶች ሸገር መፅናናትን ይመኛል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን የመከላከያ ስምምነቶችና የፖለቲካዊ ድጋፎች

በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን የጸጥታ ስጋት ተከትሎ፣ ጣሊያን ለባህረ...

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ”ንዋይ” የተሰኘ መተግበሪያን ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎች...

የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ እንግልት እየዳረገ ነው

በአዲስ አበባ እና በልዩ ልዩ የክልል ከተሞች የሚስተዋለው የነዳጅ...

ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሀዘናቸውን ገለጹ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም...