“እስራኤል ከደቡባዊ ሊባኖስ እስክትወጣ ትጥቅ አንፈታም”

Date:

  • ሂዝቦላህ

ሂዝቦላህ፣ እስራኤል ከደቡባዊ ሊባኖስ እስክትወጣ ድረስ ትጥቅ እንደማይፈታ ማስታወቁን አልጀዚራ እና አል አረቢያ ዘግበዋል።

የሂዝቦላህ ዋና ፀሃፊ ነኢም ቃሲም ለአል አረቢያ እንደተናገሩት የአሜሪካ እና የእስራኤል ዛቻ ፓርቲያቸውን “እጅ እንዲሰጥ” ወይም የጦር መሳሪያ እንዲፈታ አይገፋፋውም።

ዋና ፀሃፊው በቴሌቭዥን ባደረጉት ንግግር “ይህ ማስፈራሪያ እጅ እንድንሰጥ አያደርገንም፤ በሊባኖስ እና በአካባቢው የሚደረገውን ወረራ ህጋዊ የማድረግ አካል አንሆንም” ብለዋል።

ዋና ፀሃፊው ሂዝቦላህ ለሰላም በሩ ክፍት መሆኑን ጠቅሰው፤ ነገር ግን ኢስራኤል የአየር ወረራዋን እስክታቆም እና ከደቡብ ሊባኖስ እስክትወጣ ድረስ ትጥቅ አንፈታም ብለዋል። እስራኤልን ከመጋፈጥም ወደኋላ አንልም ሲሉም ገልጸዋል።

ይህ ሁኔታ የቀጣናውን ውጥረት ሊያባብሰው ይችላል ተብሏል። ሂዝቦላህ እና እስራኤልም ወደ ከፍተኛ ግጭት ሊያመሩ እንደሚችሉ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...