ከቱሪዝም ዘርፍ 4 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ገቢ ተገኘ

Date:

ባለፉት 11 ወራት ከቱሪዝም ዘርፍ 4 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ገቢ መገኘቱን የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለፁ።

በዚህ ዓመት ከቱሪዝም ዘርፉ 5 ቢሊዮን ብር ለማግኘት ታቅዶ ከዚህ ውስጥ 4.8 ቢሊዮን ብር ማሳካት መቻሉን ሚኒስትሯ ተናግረዋል።

ዘርፉ ማክሮ ኢኮኖሚ ላይ ሶስት በመቶ አስተዋጽኦ ማድረጉን እና በፊት የነበረው አንድ ሚሊየን የማይሞላ ዓመታዊ የቱሪስት መጠን አሁን ላይ ቁጥሩ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ገልፀዋል።

ከኮቪድ ጋር ተያይዞ የነበረው የእንቅስቃሴ ገደብ የታመቀ የመንቀሳቀስ፣ የመጎብኘትና አዳዲስ ቦታዎችን የማየት ፍላጎት ፈጥሯል ያሉት ሚኒስትሯ፤ በዚህም ዘርፉ ላይ ያለዉን ፍላጎት በማየት በትኩረት በመሰራቱ የቱሪስት ቁጥር መጨመር መቻሉን አንስተዋል።

ቱሪዝም ከጉብኝት በላይ ነው፤ በተዋወቅን ቁጥር አንዱ ስለአንዱ ማሰብ ይመጣል ለጠንካራ ሀገር ግንባታ ቱሪዝም ትልቁን ሚና ይወስዳልም ነው ያሉት ሚኒስትሯ።

እንደ ሀገር ኢንቨስት የሚደረግበት የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት ከቱሪዝም መዳረሻነት ባሻገር ሀገራዊ መግባባት ለማምጣት አስተዋጽኦ እንደሚያደርግም ገልፀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...