ከ100 የሚበልጡ ስደተኞች በሜድትራንያን ባህር ላይ ህይወታቸው አለፈ

Date:

117 ሰዎችን ጭኖ ከሊቢያ በመነሳት አውሮፓ ለመድረስ የሞከረ መርከብ ከሰጠመ በኋላ 116 ሰዎች ሲሞቱ በህይወት የተረፈው አንዱ ብቻ ነው።

አደጋው ባለፈው ሳምንት ማጋጠሙ የተዘገበ ሲሆን በህይወት የተረፈው ግለሰብ ወደ ሆስፒታል መወሰዱ ተነግሯል።

በህይወት የተረፈው ግለሰብ የተገኘው አደጋው ከደረሰ ከሁለት ቀናት በኋላ ነው ሲባል ያገኙት በእንጨት በተሰራ ጀልባ አሳ የሚያጠምዱ ቱኒዛውያን ናቸው።

መርከቧ ከሊቢያ ተነስታ ጥቂት እንደተጓዘች ድጋፍ እንደሚያስፈልጋት መልዕክት ብትልክም በሳተላይትም በአየር ፍለጋም ልትገኝ አልቻለችም።

በህይወት የተረፈው ግለሰብ ከሊቢያ ጥቂት እንደተጓዙ መጥፎ የአየር ንብረት መፈጠሩን ገልጿል።

በወቅቱ በሰዓት 40 ኪሎ ሜትር የሚነፍስ ነፋስ ነበር ሲባል አደጋውም በዚህ ምክንያት እንደደረሰ ታምኗል።

ዘገባው የዴይሊ ኤክስፕረስ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...