“መንግሥት ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ዜጎች ላይ የታክስ ጫና ማብዛት የለበትም”
የኬንያ መንግሥት የኑሮ ውድነትን ለማቅለልና ኢኮኖሚውን ለማነቃቃት በማለም፣ በወር ከ30 ሺህ የኬንያ ሽልንግ ($233) በታች ገቢ ያላቸው ዜጎች ላይ የታክስ ቅነሳ ለማድረግ መወሰኑን አስታወቀ።
• የውሳኔው ዓላማ፦ የዜጎችን የተጣራ ገቢ (Take-home pay) በመጨመር የዕለት ተዕለት ወጪያቸውን እንዲሸፍኑ መርዳት።
• የሚኒስትሩ እይታ፦ የገንዘብ ሚኒስትሩ ጆን ምባዲ “ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች ለቤት ኪራይና ለትራንስፖርት ከከፈሉ በኋላ በእጃቸው ምንም አይቀራቸውም” በማለት የታክሱን አስፈላጊነት አስረድተዋል።
• ከፍተኛ ለውጥ፦ ይህ እርምጃ የመጣው የኬንያ ገቢዎች ባለሥልጣን የታክስ አሰባሰቡን ለማጥበቅና አዳዲስ አሠራሮችን ተግባራዊ እያደረገ ባለበት ወቅት ነው።
የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ጆን ምባዲ፣ “መንግሥት ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ዜጎች ላይ የታክስ ጫና ማብዛት የለበትም” ብለዋል፡፡
