“ወደ አሜሪካ ሲጓዙ ስማርት ስልክ አይጠቀሙ”

Date:


          
   3 የአውሮፓ ሃገራት እና ካናዳ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ  ዚጎቻቸው ስማርት ስልኮችን እንዳይጠቀሙ ፥ ይልቁንም በርነር ስልኮችን በመያዝ ራሳቸውን እንዲጠብቁ አሳሰቡ፥ወደ አሜሪካ በሚገቡ ሰዎች ላይ ስልክና ላፕቶፕን ጨምሮ በኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶች ላይ የሚደረገው ምርመራ ተጓዦች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ እያደረገ እና መጉላላትን እየፈጠረ በመሆኑ ይህንን ለመከላከል ስማርት ያልሆነውን በርነር ስልክ እንዲጠቀሙ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

ከዚህም በተጨማሪ በርነር ሥልክ የማይጠቀሙ እና ስማርት ስልኮችን ይዘው የሚጓዙ ከዲጅታል አካውንታቸው ማለትም ኢሜልና ማህበራዊ ገፆቻቸውን ሳይን አውት እንዲያደርጉ ማሰሰቢያ ተሰጥቷል።

በርነር ስልኮች የድምጽ እና ጽሁፍ መልዕክት ብቻ የሚያስተላልፉ ፣ኢንተርኔት መጠቀም የማይችሉ ራስን ከክትትል የሚጠብቁ በየሱቁ የሚገኙ ርካሽ ስልኮች ሲሆኑ ፣በርነር የሚል ስያሜ ያገኙትም ግዚያዊ እና ተግባራቸውን እንደፈጸሙ የሚጣሉ ወይንም የሚቃጠሉ በመሆናቸው እንደሆንም መረዳት ተችሏል።

ከካናዳ በተጨማሪ ይህንን ማሳሰቢያ ወደ አሜሪካ ለሚጓዙ ዜጎቻቸው  ያወጡት ሃገራት ፈረንሳይ ፥ ጀርመን እና ዴንማርክ ሲሆኑ፥በትራምፕ አስተዳደር ላይ ትችት የሰነዘሩ እና ለስብሰባ ወደ አሜሪካ የተጓዙ ፈረንሳዊ  ሳይንቲስት ስልካቸው ላይ ትችታቸው በመገኘቱ ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ መደረጋቸውን ትራቭል እንድ ቱር ዎርልድ ዛሬ እንደ አውሮፓውያነ (-April 18/2025)

ሉዓላዊ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...