በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል የኤርትራ ድንበር ላይ የወርቅ ማዕድን እንዲሁም የዕጣን ዛፎች በብዛት ከሚገኙበት ቃፍታ ብሄራዊ ፓርክ ወደ 12 ሺህ ህገ-ወጥ የወርቅ ማዕድን አውጭዎችን ማስወጣቱን የኢትጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን አስታውቋል፡፡
እና እጣን አምራቾች ደኖችን እያወደሙ ፈተና እንደሆነበት የኢትጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ገልጽዋል፡፡
ባለፈው ቅዳሜ ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ 12 ሺህ የሚሆኑ ህገ-ወጥ ወርቅ አውጭዎችን በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እና በሌሎችም የፀጥታ ሀይሎች እገዛ ከፓርኩ እንዲወጡ መደረጉን የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን መኮንን ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
በተመሳሳይም ከዚህ በፊት ወደ 12 ሺ የሚሆኑ ህገ ወጥ እጣን አምራቾችን ከፓርኩ እንዲወጡ መደረጉን ያስታወሱት ዋና ዳይሬክተሩ በአካባቢው የምንቀሳቀሱ ህገ ወጥ ወርቅ አውጭዎችም ለፓርኩ ፈተና ሆነውበታል ብለዋል፡፡
በፓርኮች ውስጥ ማዕድን ማውጣት እና የእርሻ ስራ ማከናወን በአዋጅ የተከለከለ ቢሆንም ህገ-ወጥ የወርቅ አውጭዎች እና የእጣን አምራቾች ግን ወደ ቃፍታ ብሄራዊ ፓርክ በተደጋጋሚ እየገቡ እንደሚያዙ ነው የገለፁት፡፡ ይህንን ተከትሎም እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በሰሜኑ ጦርነት ፓርኩ ተጎድቶ እንደነበር እና ከ2015 እስከ 2017 በተሰራው ስራ ወደ ኤርትራ የተሰደዱ ዝሆኖች ወደ ፓርኩ መመለሳቸውን አሐዱ መዘገቡ ይታወሳል፡፡
